የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ታዬ አፅቀ-ሥላሴ የጥራት መንደርን ጎበኙ፡፡
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 1/2017 ዓ.ም (ኢስኢ) በቅርቡ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ የተመረቀውን የጥራት መንደር የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ታዬ አፅቀ-ሥላሴ ዛሬ ጎብኝተዋል፡፡
ክቡር ፕሬዝዳንቱና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት ላብራቶሪዎችና ወርክሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ድኤታ ክቡር አቶ እንዳለው መኮንን እና የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሙሉጌታ ደርበው እንዲሁም የስራ ክፍል ኃላፊዎች ስለሚሰጡት አገልግሎት ገለፃ አድርገውላቸዋል፡፡